ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር በኃጢአት ለወደቀው አዳም የገባለት ቃል ኪዳን « ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ» የሚል እንደነበር ሁሉ ለታላቁ የሃይማኖት አባት አብርሃምም እንደዚሁ «በዘርህ አህዛብ ይበረካሉ» የሚል ቃልኪዳን ገብቶለት ነበር ዘፍ፤12፤2-3 የሐ.ስራ 3፤25 የሰጠውን ቃል ኪዳን የማያስቀር አምላክ ጊዜው ሲደርስ ፈፀመው። መቼም ፍጥረት ያለ ታሪክ ታሪክም ያለፍጥረት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፤ ስለዚህ በደግነትም ሆነ በክፋት ብዙም ሆነ ጥቂት ታሪክ የሌለው ፍጥረት የለም። ይህንን ለማለት የተፈለገው በንፅህናዋ ያለተጓዳኝ ተፈጥራ ብቻዋን የኖረች የወላደተ አምላክ ልደት እንደ እርሷ ክብር ሳይሆን በመጠኑ ለማስታወስ ተፈልጐ ነው።
ያንብቡ › |